ስለ እኛ

ራዕይ

1.ራዕይ 2018 ከተስፋ ወደ ሚጨበጥ ብረሀን
2. ራዕይ 2023 የአፍሪካ ብልፅግና ተምሳሌት
3. ራዕይ 2040 አለም አቀፍ የብልፅግና አርአያ

ዓላማ

“የበለጸገች ኢትዮጵያን እውን ማድረግ”
ስለ እኛ

የብልጽግና ፓርቲ አመሰራረት

ብልፅግና ፓርቲ  ሶስት የቀድሞ የኢህአዴግ አባል ታርቲዎች የአማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (አዴፓ)፤ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኦዴፓ) እና የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ደኢህዴን) እንዲሁም አፋር ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (አፍዴፓ) ፤ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ዴሞክራሲያዊ አንድነት ግንባር (ቤጉህዴፓ) ፤ የኢትዮጵያ ሶማሌ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢሶህዴፓ) ፤ የጋምቤላ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ጋህዴን) እና የሀረሪ ብሔራዊ  ሊግ (ሀብሊ) በመካተት ህዳር 2012 ዓ.ም ተመሰረተ።

በሀዋሳው የኢህአዴግ 11ኛ መደበኛ ጉባዔ የፓርቲ ውሕደት በመዘግየቱ በፍጥነት እንዲጠና ተወሰነ

የብልፅግና ፓርቲ መለያ እሴቶች

ህብረ ብሔራዊ አንድነት

አንድ የፖለቲካና ኢኮኖሚ ማህበረሰብ መገንባት ነው፡፡ ህብረ ብሔራዊ ስንል የብሔር፣ የሐይማኖት ወይም ሌላ ማንነቶችን ያቀፈና ማንንም ያላገለለ ማህበረሰብ ማለታችን ነው፡፡

የዜጎች ክብር

ኢትዮጵያዊያንን በእኩል ዓይን የሚያይና የሚዳኝ፣ ፍትሃዊ ተጠቃሚነታቸውን የሚያረጋግጥ፣ የብሔር ብሔረሰቦች መብትና ነጻነት የሚረጋገጥበት፣ እውነተኛ ህብረ ብሔራዊነት የሚረጋገጥበት፣ በዋና ዋና የሀገሪቱ ጉዳዮች ላይ ሁሉም ዜጋ ውሳኔ ላይ ተሳታፊ የሚሆንበት፣ የሀብት ስልጣንና የመብት ክፍፍሉ ፍትሃዊ የሚሆንበት የፖለቲካዊ ኢኮኖሚ ስርዓት መፍጠር፣ አንድ የፖለቲካና ኢኮኖሚ ማህበረሰብ መገንባት፡፡

ነጻነት

ዜጎች የራሳቸውን ህይወት ርዕይ የመምረጥ፣ በመረጡት መንገድ የመኖር መብት እንዲረጋገጥ ማድረግ፡፡ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተሳትፎ በማሳደግ የሀገራችንን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች በዘላቂነት መፍታት፡፡ የዜጎችን የመሰብሰብ፣ የመደራጀት፣ የመጻፍና ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ፣ የመምረጥና የመመረጥ መብቶችን ማረጋገጥ፡፡

የፓርቲ አባላት